በሰሜን አሜሪካ የጽርሐ ጽዮን ፕሮጀክት አሥተባባሪ ኮሚቴ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርርስቲያን ከ፵፭ ሚሊዮን በላይ የእምነቱ ተከታይ ምእመናንና ምእመናት፣ ከ፵ ሺህ በላይ ገዳማት፣ አድባራትና የገጠር አቢያተ ክርስቲያናት፣ ከ፭፻ ሺህ ያላነሱ ካህናት እና ፮ ነጥብ ፭ ሚሊዮን የሚሆኑ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሲኖሯት፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ በድምሩ በ፶፭ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት መዋቅሯን ዘርግታ ታስተዳድራለች ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከአሏት አህጉረ ስብከት አንዱ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ነው፡፡

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ጥንታውያን ገዳማትና አድባራት፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች፤ ጥንታውያን የቤተ ክርስቲያን ቤተ መዘክሮች (የቤተ ክርስቲያን ግምጃ ቤቶች)፤ የአጽመ ነገሥታት፤ የአጽመ ቅዱሳን ማረፊያ፣ በአጠቃላይ ዓለምን የሚያስደንቁ የቱሪስት መስህብ የሆኑ ገዳማትንና ወዘተ የሚገኙበትና በስሩም የሚያስተዳድራቸው ፰ የአንድነት ገዳማት፤ ፴፰ አድባራት፤ ፴፪ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት በድምሩ ፸፰፣ በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ካህናት፣የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች፣ምእመናንና ምእመናት የሚገኙበት ሀገረ ስብከት ነው፡፡

ስለሆነም ከላይ የተዘረዘሩት የቤተ ክርስቲያኒቱ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች ያሏት ቤተ ክርስቲያን ታሪኳንና ትውፊቷን ጠብቃ ለቀጣዩ ትውልድ እንድታስረክብ አርቆ በማሰብ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የቤተ ክርስቲያንን ትውፊት የሚገልጽ ደረጃውን የጠበቀ የሕንፃ ግንባታ ሥራ ለመሥራት ”የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ጽርሐ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም መንበረ ጵጵስና የሕንፃ ግንባታ ሥራ” በሚል ስያሜ ስለሕንፃ ግንባታው ሥራ በዝርዝር ተዘጋጅቶ ለመንግሥት ካቀረበ በኋላ ኃሳቡ ተቀባይነት አግኝቶ የሕንፃ ግንባታውን ለማስፈጸም ፵፪ ሸህ ካሬ ሜትር  ስፋት ያለው መሬት ለዚሁ ሥራ የሚውል ሀገረ ስብከቱ ከመንግሥት ተረክቧል፡፡

ስለሆነም የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም የሕንፃ ሥራዎችን የሚያስፈጽሙ ጠቅላላ ኮምቴ ፤ የሥራ አስፈጻሚ ዓቢይ ኮሚቴ እና ንዑሳን ኮሚቴዎችን በሊቀ ጳጳሱ መሪነት አቋቁሞ የሕንፃ ሥራ አስፈጻሚ ዓቢይ ኮሚቴውም ሆነ ንዑሳን ኮሚቴዎች ሥራዎችን በሥርዓትና በተደራጀ መልኩ መምራት ይችሉ ዘንድ የሥራ አስፈጻሚ ኪሚቴ ካወቀረ በኃላ በተጓዳኝ የሃገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ወደ ሰሜን አሜሪካ በሥራ በመጡበት ወቅት የሰሜን አሜሪካ ሕንጻ ግንባታ እና የገቢ አሰባሳቢ የውጪ አሰባሳቢ ኮሚቴ ማዋቀር አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ፤ አብይ ኮሚቴው በዋሺንግተን ዲሲ በታሕሳስ ፳፻፲፩ ዓም ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕርዳር ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት የውጪው አብይ ኮሚቴ ሊቋቋም ችሏል።

ተጨማሪ መረጃ

ጥቂት በመለገስሥራውን እውን ያድርጉ

በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሚሰራውን የጽርሐ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ግንባታ ለማከናወን በብፁዕ አቡነ አብርሃም መሪነት የተጀመረው ፕሮጀክት በረጅም ጊዜ ስትራቴጂ፣ እቅድና ፕላን ተመርኩዞ ሥራውን ማቀላጠፍ ከጀመረ ውሎ አድሯል። ይህ ፕሮጀክት በአይነቱ ለየት ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪክ፣ አስተምህሮ፣ ብሎም ቤተ ክርስቲያኒቱ የደረሰችበትን ደረጃ ከግምት በማስገባት በደረጃው ከፍ ያለ ካቴድራል፣ የግዕዝ ዩኒቨርሲቲ፣ የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት፣ የካህናትና አገልጋዮች ማሠልጠኛ፣ የእንግዶች ማረፊያ፣ የአብነት ትምህርት ቤት፣ ቤተ መዘክር፣ ቤተ መጻሕፍት ብሎም የቤተ ክርስቲያኗን አገልግሎት የሚደግፉ የዕደ-ጥበብ ሥራ ማከናወኛ ተቋማትን ለመገንባት የታሰበ መጠነ ሰፊ ፕሮጀክት ነው።እርስዎም የበኩሎዎትን ለማበርከት አሁኑኑ ቤተሰባችን ይሁኑ።

አስተያየቶች

በመላው ዓለም ያሉ ለጋሾቻችን ምን እያሉ ነው

ይሄንን ፕሮጀክት በመጀመሪያ በዩቲብ ስመለከት ማመን ነው ያቃተኝ፣ እንደ ሰው ተጠራጥሬም ነበር እውን ይሄን ያህል ሜጋ ፕሮጀክት በኢትዮጵያውያን ይሠራል? እውን ብፁዕነታቸው እድሜውን ሰጥቷቸው ያስጨርሱት ይሆን ብዬ ትንሽ በልቤ ጥርጣሬ ገብቶኝ ነበር፣ ምክንያቱም ከዚህ በፊት የምናውቃቸው ትላልቅ ቤተክርስቲያናት 30 ዓመት ፈጀባቸው ለመጨረስ ሲባል ሰምቻለሁ ታዲያ ዛሬ ላይ የሥራዎቹ ወደ 50% በአንድ ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ስሰማ ስለእውነት በራሴ መጠራጠር አፈርኩ፣ እራሴንም ከአሁን በኃላ ይሄ ፕሮጀክት እስከሚጠናቀቅ እና እስኪጀመር አብሬ ለመሥራት ለማገዝ ቃለ ገባቡኝ፤ ከዚህ በኃላ በኃላ ወንበር ቁጭ ብለን መተቸት ሳይሆን አብሮ መሥራት ብቸኛው አማራጭ መሆኑን የተማርኩበት ፕሮጀክት ነው፤ ይህን ሃሳብ ያመነጩትን ወንድሞች እህቶች አባቶች እግዚአብሔር አምላክ እድሜውን ያበድራችሁ፤ ተጨማሪ እድሜ ሰጥቷችሁ እስከ መጨረሻዋ ድረስ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ትንሳኤ ያሳያችሁ ለእኛም ለምንጠራጠረው ልቦናውን ይክፈትልን በማለት አጠቃልላለሁ፤

ተድባበ ማርያም ከቤልጄም ደች ላንድ

ወ ጊዜ ለኩሉ” ይባላል እኮ ወንድሞቼ ጊዜው ደርሶ የግዕዝ ዩኒቨርስቲ በኦርቶዶክሳውያን ብርታት ሊገነባ መሆኑስ ስሰማ የተሰማኝን ልነግራችሁ አልችልም፤ ምክንያቱም ቀደምት አባቶቻችን ቀድመው የቤተክርስቲያናችንን ትምህርቶች በሙሉ፣ መጻሕፍቱን፣ ብራናውን፣ ዜማውን፣ ዜና መዋዕሉን፣ ገድላቱን በሙሉ በትላልቅ መጻሕፍት ደጉሰው ሰንደው ለእኛ ለልጆቻቸው አውርሰውን አልፈው ነበር፤ ነገር ግን የእኛ ትውልድ ሌላ መሥራት ባንችል እነዚህ ጥንታውያን አባቶቻችን ያስቀመጡልንን ማቆየት አቅቶን ለብዙ ውድቀት ተዳርገናል፤ አሁን ግን እንደ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ያሉ የአባቶቻቸው ልጆች ይህንን ይዘው መምጣታቸው ሁሌም ቤተክርስቲያን ስታስባቸው ይኖራሉ፤ እድሜ ይስጥልን አባታችን በረከትዎ ይደርብን አሜን

አምኃሥላሴ ከካሊፎርኒያ ሎስ አንጀለስ

የጽርሐ ጽዮን ፕሮጀክት እጅግ በጣም ለሃገር ፣ ለወገን፣ እንዲሁም ለቅድስት ቤተክርስቲያን እጅግ በጣም ጠቃሚ እና መጪው ትውልድ ሊቀርጽ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ወደ ቀደመ ክብሯ ሊመልስ የሚችል ትልቅ ፕሮጀክት ነው። የተጀመረውን የማስጨረስ የእኛ እና የእኛ ብቻ ነው ያንንም ማድረግ ሃላፊነታችን ባቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር ነው እላለሁ፤

ሰውማነህ ከጅማ

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የልማት አባት ናቸው፣ በቅዱስ ራጉኤል ቤተክርሲትያን የሠሩት ትውልድ የሚያንጽ ሥራ በቅድስት ቤተክርሲትያናችን ዘወትር ሲወሳ ይኖራል፤ አሁንም በባሕር ዳር የጀመሩት መጠነ ሰፊ ፕሮጀክት የዚህ የቅዱስ ራጉኤል ሥራቸው ተከታዩ ክፍል ነው፤ እስከ መጨረሻው የብፁዕ አባቻንን ሥራ በጋራ ሆነን መጨረስ እና ማስፈጸም ከሁላችህም የሚጠበቅ ሃላፊነት ነው እላለሁ፤

ኃይለመለኮት ከፍሎሪዳ

የግዕዝ ዩኒቨርስቲ? ማን ያስበዋል እጅግ ትልቅ እና መሠረታዊ ሃሳብ ለሃገራችን የሚያስፈልግ፡ ቤተክርስቲያን ዛሬ ለደረሰችበት ችግር የደረስነው የቀደሙት አባቶቻችን የግዕዝ ዩኒቨርስቲን የመሰሉ የቀደሙትን እሴቶቻችንን ሊጠብቅ እና ሊያስቀጥል ባለመቻላቸው ይመስለኛል፤ አሁን ግን ጥብአት ያላቸው አባቶቻችን በመነሳታችው እንዲህ አይነት ሃሳቦች የብዙዎችን ልብ በመግዛቱ ዛሬ ላይ የጽርሐ ጽዮንን ሥራ ለመጨረስ በመቃረቡ፣ ደስታችን እጥፍ ድርብ ነው፣ ይበል ብለናል እኛም የምንችለውን እናደርጋለን በርቱልን::

መላኩ ከሎንዶን

እነዚህን ተስፋ ሰጭ ፕሮጅክቶች ለመደገፍ አሁኑ ይርዱ

Bitnami