በዚህ በሰሜን አሜሪካ የተመረጠው አብይ ኮሚቴው በቀጥታ ተጠሪነቱ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ሆኖ፤ የሥራ አስፈጻሚ ዓቢይ ኮሚቴው ደግሞ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው የመማክርት ጉባኤ በመሪነት የሚመራ ሲሆን ፤ በእያንዳንዱ የሥራ አስፈጻሚ አባል ስር ንዑሳን ኮሚቴዎች ተቋቁመው ንዑሳን ኮሚቴዎች በሥራ አስፈጸሚ የክፍል ኃላፊዎች ሰብሳቢነት ይመራሉ፡፡ የሥራ አስፈጻሚ ዓቢይ ኮሚቴ አባላት በሥራቸው ከ3-5 ከዚያም በላይ አባላት የያዙ ንዑሳን ኮሚቴዎች ይኖራሉ፡፡ ይህ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በየወሩ ወይም እንደ አስፈላጊነቱ አስቸኳይ ስብሰባ የሚያደርግ ሲሆን ኮሚቴዉ ፲፩ አባላት ይኖሩታል:: እነዚህም፡-

ሀ. ሊቀመንበር                                                      ረ. የሕዝብ ግንኙነት፤

ለ. ም/ሊቀመንበር                                                ሰ. የኢንጂነሪንግ እና የግንባታ ክትትል ክፍል

ሐ. ጸሐፊ                                                              ሸ. የሕግ ክፍል

መ. የፋይናንስ ክፍል                                             ቀ. የሚዲያና ኢንፎርሜሽን ክፍል

ሠ. የገንዘብ አሰባሳቢ ክፍል                                   በ. የእቅድ እና ልማት ክፍል

ግብረ ኃይሎቻችን

እነዚህ በጎፈቃደኞች ራዕዮን ተግባራዊ እያደረጉ ነው
አቶ ዮሴፍ ወንድሙ
አቶ ዮሴፍ ወንድሙ
ምህንድስና ክፍል ኃላፊ
ዶ/ር እልልታ ረጋሳ
ዶ/ር እልልታ ረጋሳ
ህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ
ዲ/ን ዶ/ር ግዛቸው ጊያ
ዲ/ን ዶ/ር ግዛቸው ጊያ
የፕሮጀክቶች አማካሪ
አቶ ሲሳይ ይመር
አቶ ሲሳይ ይመር
የሂሳብ ክፍል ኃላፊ
አቶ ሰሎሞን በቀለ
አቶ ሰሎሞን በቀለ
ም/ሰብሳቢና የህግ ክፍል ኃላፊ
ዶ/ር ኢሳያስ አባቡ
ዶ/ር ኢሳያስ አባቡ
ህንጻ ዲዛይን ክፍል ኃላፊ
አቶ ወንድወሰን ኃይሉ
አቶ ወንድወሰን ኃይሉ
የዕቅድና ልማት ክፍል ኃላፊ
አቶ ሳምሶን አግዴ
አቶ ሳምሶን አግዴ
ጸሐፊና የጽሕፈት ቤት ክፍል ኃላፊ
አቶ ተክሌ አየለ
አቶ ተክሌ አየለ
ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍል ኃላፊ
አቶ አቤል ጋሼ
አቶ አቤል ጋሼ
የጽርሐ ጽዮን ሰብሳቢ

ብዙ ድጋፎች አግኝተናል

እግዚአብሔር ደጎችን ያብዛልን
0
ሙያዊ ድጋፍ

በህንጻ ዲዛይን፣ በምህንድስና፣ በሕግ፣ በአካውንቲንግ፣ በፋይናንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና በሚዲያ ወዘተ በርካታ ድጋፎችን አግኝተናል። እርስዎም ይቀላቀሉን።

0
የማቴሪያል ድጋፍ

ብዙ ቅን ምዕመናን የተለያዩ የኮንስትራክሽን ግባቶችን ለምሳሌ አሸዋ፣ ስሚንቶ፣ ብረት ወዘተ በመለገስ ብዙ አስተዋጽኦ አድርገውልናል። እርስዎም የበኩልዎን ያበርክቱ።

0
የገንዘብ ድጋፍ

በሰሜን አሜሪካ ብቻ ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናትና ምዕመናን ከተለያዩ ስቴቶች ወደ $400,000 የሚጠጋ የገንዘብ ድጋፍ አግኝተናል። እርስዎም የድርሻዎን ይወጡ።

0
የሎጂስቲክስ ድጋፍ

በኢትዮጵያ ትጉህና ቀና የሆኑ ምዕመናን ለአሸዋ፣ ስሚንቶ እና ብረት ማመላለሻ የጭነት መኪናዎችን እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶችን በመለገስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። እርስዎም ያግዙ።

አስተያየቶች

በመላው ዓለም ያሉ ለጋሾቻችን ምን ይላሉ

ይሄንን ፕሮጀክት በመጀመሪያ በዩቲብ ስመለከት ማመን ነው ያቃተኝ፣ እንደ ሰው ተጠራጥሬም ነበር እውን ይሄን ያህል ሜጋ ፕሮጀክት በኢትዮጵያውያን ይሠራል? እውን ብፁዕነታቸው እድሜውን ሰጥቷቸው ያስጨርሱት ይሆን ብዬ ትንሽ በልቤ ጥርጣሬ ገብቶኝ ነበር፣ ምክንያቱም ከዚህ በፊት የምናውቃቸው ትላልቅ ቤተክርስቲያናት 30 ዓመት ፈጀባቸው ለመጨረስ ሲባል ሰምቻለሁ ታዲያ ዛሬ ላይ የሥራዎቹ ወደ 50% በአንድ ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ስሰማ ስለእውነት በራሴ መጠራጠር አፈርኩ፣ እራሴንም ከአሁን በኃላ ይሄ ፕሮጀክት እስከሚጠናቀቅ እና እስኪጀመር አብሬ ለመሥራት ለማገዝ ቃለ ገባቡኝ፤ ከዚህ በኃላ በኃላ ወንበር ቁጭ ብለን መተቸት ሳይሆን አብሮ መሥራት ብቸኛው አማራጭ መሆኑን የተማርኩበት ፕሮጀክት ነው፤ ይህን ሃሳብ ያመነጩትን ወንድሞች እህቶች አባቶች እግዚአብሔር አምላክ እድሜውን ያበድራችሁ፤ ተጨማሪ እድሜ ሰጥቷችሁ እስከ መጨረሻዋ ድረስ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ትንሳኤ ያሳያችሁ ለእኛም ለምንጠራጠረው ልቦናውን ይክፈትልን በማለት አጠቃልላለሁ፤

ተድባበ ማርያም ከቤልጄም ደች ላንድ

ወ ጊዜ ለኩሉ” ይባላል እኮ ወንድሞቼ ጊዜው ደርሶ የግዕዝ ዩኒቨርስቲ በኦርቶዶክሳውያን ብርታት ሊገነባ መሆኑስ ስሰማ የተሰማኝን ልነግራችሁ አልችልም፤ ምክንያቱም ቀደምት አባቶቻችን ቀድመው የቤተክርስቲያናችንን ትምህርቶች በሙሉ፣ መጻሕፍቱን፣ ብራናውን፣ ዜማውን፣ ዜና መዋዕሉን፣ ገድላቱን በሙሉ በትላልቅ መጻሕፍት ደጉሰው ሰንደው ለእኛ ለልጆቻቸው አውርሰውን አልፈው ነበር፤ ነገር ግን የእኛ ትውልድ ሌላ መሥራት ባንችል እነዚህ ጥንታውያን አባቶቻችን ያስቀመጡልንን ማቆየት አቅቶን ለብዙ ውድቀት ተዳርገናል፤ አሁን ግን እንደ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ያሉ የአባቶቻቸው ልጆች ይህንን ይዘው መምጣታቸው ሁሌም ቤተክርስቲያን ስታስባቸው ይኖራሉ፤ እድሜ ይስጥልን አባታችን በረከትዎ ይደርብን አሜን

አምኃሥላሴ ከካሊፎርኒያ ሎስ አንጀለስ

የጽርሐ ጽዮን ፕሮጀክት እጅግ በጣም ለሃገር ፣ ለወገን፣ እንዲሁም ለቅድስት ቤተክርስቲያን እጅግ በጣም ጠቃሚ እና መጪው ትውልድ ሊቀርጽ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ወደ ቀደመ ክብሯ ሊመልስ የሚችል ትልቅ ፕሮጀክት ነው። የተጀመረውን የማስጨረስ የእኛ እና የእኛ ብቻ ነው ያንንም ማድረግ ሃላፊነታችን ባቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር ነው እላለሁ፤

ሰውማነህ ከጅማ
Bitnami