Our Goal

Below is the progress of our charity campaign to support local projects related to ecology and human rights.

$10 of $100,000 raised

My Donations

Here you can view your donations made to support our projects.

Please verify your email to access your donation history.

ቤተ መዘክር

በጽርሐ ጽዮን ፕሮጀክት ውስጥ ከሚታቀፉ ጠቃሚ ፕሮጀክት ውስጥ አንዱ ቤተ መዘክር ነው፡፡ ይህ ቤተመዘክር የቤተ ክርስቲያኗን የረጅም ታሪክ ማስጎበኛና ማስተማሪያ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከክርስትና ኃይማኖት ከተጀመረበት ጊዜ በፊት ጀምሮ ታሪክ ያላት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ዛሬ በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ በአምልኮት ስርዓት ውስጥ የሚታቀፉት ጽላቶች ከእስራኤላውያን ታሪክ ከሙሴ ዘመን ጋር በእጅጉ የተያያዙ እንደመሆናቸው ቤተ ክርስቲያኗ ይኸንን የረጅም ዘመን ታሪኳን ለዘመኑ በሚመጥን መንገድ አዘጋጅታ ትውልዱ እንዲማርበት፣ ብሎም ለመጪው ትውልድ በሚገባ ተጠብቆ እንዲቆይ ለማድረግ ተገቢውን ሃላፊነት መወጣት ይኖርበታል፡፡ ይህንን ማድረግና ዘመኑን በሚገባ መዋጀት የሚቻለው ዘመኑን ያማከል ቤተ መዘክር በማደራጀት ያስፈልጋል፡፡ ይህ ፕሮጀክት በሚገባ ሲጠናቀቅ ቱሪስቶች ገዳማትን ብሎም ሀገርን ሊጎበኙ ሲመጡ የቤተክርስቲያንን፣ የሀገርን ቅርስን፣ታሪክና ባህል የሚጎበኙበትና የሚማሩበት የተዋጣለት ፕሮጀክት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

Donation form

$
Personal Info

Terms

Donation Total: $500.00